Arts TVArts TV
← NewsEconomy

ኮፊ አረቢካ በመባል የሚታወቀው የኢትዮጵያ ቡና በቻይና ገበያ ተፈላጊነቱ እያደገ ነው ተባለ

Arts TV · ማርች 18 2019

ኮፊ አረቢካ በመባል የሚታወቀው የኢትዮጵያ ቡና በቻይና ገበያ ተፈላጊነቱ እያደገ ነው ተባለ

<strong>ኮፊ</strong> <strong>አረቢካ</strong> <strong>በመባል</strong> <strong>የሚታወቀው</strong> <strong>የኢትዮጵያ</strong><strong> ቡና </strong><strong>በቻይና</strong> <strong>ገበያ</strong><strong> ተፈላጊነቱ እያደገ ነው ተባለ።</strong>rnrn&nbsp;rnrnበቻይናውያን ዘንድ ተፈላጊነቱ እየጨመረ መጥቷል የተባለው ይኸው የኢትዮጵያ ቡና ኢትዮጵያ በሃገሪቱ በተካሄደ ዓለም ዓቀፍ ልዩ የቡና ትርኢት ቀርቧል።rnrn&nbsp;rnrnኢትዮጵያ የተሳተፈችበት ይኸው አውደትርዒቱ ከመጋቢት 2 እስከ 8 ቀን 2011 ዓ.ም በቻይና ፑኤር ከተማ ተካሂዷል። እንደ ውጭ ጉዳይ ቃል አቀባይ ፅህፈት ቤት  ገለፃ በትርዒቱ ኢትዮጵያ ያላትን የተፈጥሮ ቡና  ልዩ ጣዕምና ጥራት እንዲሁም ብዝሃነት  ለቻይና ህዝብ አስታዋውቃበታለች።rnrnኮፊ አረቢካ በመባል የሚታወቀው የኢትዮጵያ በቻይና ገበያ ተመራጭ መሆኑና በቻይናውያን ዘንድ ተፈላጊነቱ እያደገ መምጣቱም በዚሁ ወቅት ተገልጿል።rnrn&nbsp;rnrnእንደ ኢትዮጵያ ያሉ ጥሬ ቡና የሚልኩ አገራት እሴት በመጨመር ቡና ለውጭ ገበያ ማቅረብ የሚያስቸሉበት ልምድም በአውደትርዒቱ ቀርቧል።rnrnከትርኢቱ ጎን ለጎን የኢትዮጵያ ልዑክ ከፑኤር ከተማ ከፍተኛ ሃላፊዎችና የዩና ግዛት ዓለም አቀፍ የቡና ገበያ ቢሮ ተወካዮች ጋር በዘርፉ በጋራ መስራት በሚቻልባቸው ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት አድርገዋል።rnrnበፕሮግራሙ ላይ ቡና በማቀነባበር፣ በማልማት፣ በማምረት፣ በመሸጥና ተያያዥ ዘርፎች የተሰማሩ ከአንድ ሺህ በላይ ተሳታፊዎች ተገኝተዋል።rnrn&nbsp;

More in Economy