ከግብር ጋር የተያያዙ 14 አዳዲስና ነባር መመርያዎች ተሻሽለው ፀደቁrnrnየገቢዎች ሚኒስቴር እና የገንዘብ ሚኒስቴር ከግብር ጋር የተያያዙ 14 አዳዲስና ነባር መመርያዎችን አሻሽለው በማፅደቅ ወደ ሥራ እንዲገቡ መወሰናቸው ተነግሯል፡፡rnrnበገቢዎች ሚኒስቴር ከወጡት መመርያዎች ውስጥ፣ ከተከፋይ ሒሳብ የንግድ ትርፍ ግብር ቀንሰው እንዲያስቀሩ ኃላፊነት የተሰጣቸው ታክስ ከፋዮችን ለመወሰን የወጣው መመርያ አንዱ ነው፡፡rnrnየንግድ ሥራ ከተቋረጠ በኋላ በተገኘ ገቢ ላይ ግብር ስለሚከፈልበት ሁኔታ በገቢዎች ሚኒስቴር መመርያ የወጣ ሲሆን፣ የታክስ ክፍያ ጊዜ ማራዘምን የተመለከተው ሚኒስቴሩ ካወጣቸው መመርያዎች ውስጥ የሚጠቀስ ነው፡፡rnrnከተከፋይ ሒሳብ ላይ ሁለት በመቶ የንግድ ትርፍ ግብር ቀንሰው እንዲያስቀሩ ኃላፊነት ከተሰጣቸው ድርጅቶችና መሥሪያ ቤቶች በተጨማሪ፣ ሰፊ የአገር ውስጥ ግብይት ላላቸው ግለሰብ ግብር ከፋዮች ኃላፊነቱን በመስጠት የሚሠራበት ይሆናል ነው የተባለው፡፡rnrnበገንዘብ ሚኒስቴር በኩል ከወጡት ስድስት መመርያዎች ውስጥ የቅድመ ግብር ክፍያ ሥርዓት አፈጻጸም፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመላሽ ስለሚሆንበት መመርያና የታክስ ከፋዩን ሀብት ስለመያዝና ስለመሸጥ የወጡት መመርያዎች ይገኙበታል፡፡rnrnከዚህ በተጨማሪ በታክስ አስተዳደር አዋጁም በድርጅቶችና መሥሪያ ቤቶች ላይ የተጣሉ አስተዳደራዊ ቅጣቶች እና የወንጀል ድንጋጌዎች ተፈጻሚ እንደሚሆኑም ማሻሻያዎቹ ላይ ተቀምጧል፡፡ ሪፖረትር እንደዘገበው፡፡
← NewsEconomy
Economy
Economy
Economy
ከግብር ጋር የተያያዙ 14 አዳዲስና ነባር መመርያዎች ተሻሽለው ፀደቁ
Arts TV · ሜይ 2 2019

More in Economy
Economyኢትዮጵያ ባለፉት አስር ወራት ከዓለም አቀፍ የፋይናንስ ተቋማት እና መንግስታት የ4.7 ቢሊዮን ዶላር የልማት ድጋፍ እንዳገኘች የገንዘብ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡
ጁን 6 2019
Economyበኮንትሮባንድ የሚሳተፉ አካላት አስተማሪ እርምጃ ሊወሰድባቸው ይገባል ተባለ፡፡
ሜይ 10 2019
ARTS
Economyከ37.4 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት ኮንትሮባንድ ማዕድናት ባለፉት ዘጠኝ መያዙን የገቢዎች ሚኒስቴር አስታወቀ ፡፡
ሜይ 7 2019
Economyየንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ለማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ ልዩ ትኩረት መስጠቱን ገለጸ፡፡
ሜይ 7 2019

