Arts TVArts TV
← NewsEconomy

ኢትዮጵያ የአፍሪካ አህጉራዊ የንግድ ቀጣና ስምምምነትን ለአፍሪካ ህብረት አቀረበች

Arts TV · ኤፕሪ 11 2019

ኢትዮጵያ የአፍሪካ አህጉራዊ የንግድ ቀጣና ስምምምነትን ለአፍሪካ ህብረት አቀረበችrnኢትዮጵያ በቅርቡ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በኩል ያጸደቀችውን የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና ስምምነት  ለአፍራካ ህብረት ገቢ አድርጋለች።rnrnበፕሮግራሙ ላይ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽነር ሙሳ ፋኪ ማህማት፣ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዋና አማካሪ አቶ ማሞ ምህረቱ እና በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካና የመካከለኛው ምስራቅ አገራት ቋሚ ተጠሪ አምባሳደር ወይንሸት ታደሰ ተገኝተዋል።rnrnየህብረቱ ሊቀመንበር ሙሳ ፋኪ ማህማት በዚሁ ወቅት እንዳሉት የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና የኢንዱስትሪ እና የተቋማትን ተወዳዳሪነት በማሳደግ በአህጉሩ ያሉ የገበያ እድሎችን አሟጦ ለመጠቀምና ሃብቶችን በአስፈላጊ አካባቢዎች እንዲገኙ ለማድረግ ያስችላል ብለዋል።rnrnየ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ዋና አማካሪ አቶ ማሞ ምህረቱ በበኩላቸው ውሳኔው ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ ጠንካራ ቀጣናዊ ትስስር እንዲኖርና ነጻ የሰዎችና የሃሰብ ዝውውር እንዲስፋፋ ካላቸው ራዕይ ጋር የሚጣጣም መሆኑን ገልጸዋል።rnrnየአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ስምምነት በአፍሪካውያን መካከል ያለውን ንግድ እንደሚያሳድገው፤ በቀጣናዊ የንግድ ማህበረሰቦች መካከል ብሎም በአህጉር ደረጃ የበለጠ ትስስር እንዲኖር ያስችላል ብለዋል።rnrnስምምነቱ ከዓለም የንግድ ድርጅት ስምምነት ከተፈረመ ወዲህ በአፍሪካ ትልቁ የንግድ ስምምነት ይሆናል።rnrnመረጃው የውጭ ጉዳይ ቃል አቀባይ ፅህፈት ቤት ነውrnrn 

More in Economy