Arts TVArts TV
← NewsEconomy

ቦይንግ ከኢትዮጵያ አየር መንገዱ አደጋ ጋር በተያያዘ እየተከሰሰ ነው

Arts TV · ኤፕሪ 1 2019

ቦይንግ ከኢትዮጵያ አየር መንገዱ አደጋ ጋር በተያያዘ እየተከሰሰ ነው

ቦይንግ ከኢትዮጵያ አየር መንገዱ አደጋ ጋር በተያያዘ እየተከሰሰ ነውrnrnበኢትዮጵያ አየር መንገዱ አደጋ ህይወቱን ያጣ አንድ ግለሰብ ቤተሰቦች በአውሮፕላኑ አምራች ኩባንያ ቦይንግ ላይ በአሜሪካ የፌደራል ፍርድ ቤት ክስ መመስረታቸው ተሰምቷል።rnrnበአደጋው ህይወቱ ያለፈው ጃክሰን ሙሶኒ የሚባል ሩዋንዳዊ ግለሰብ ዘመዶች ናቸው በቦይንግ ላይ ክሱን የመሰረቱት፡፡rnrnየግለሰቡ ቤተሰቦች በክሳቸው ላይ አደጋው የደረሰበት ቦይንግ 737 ማክስ ኤት አውሮፕላን በአውቶማቲክ የበረራ መቆጣጠሪያ ሥርዓቱ ላይ የዲዛይን ችግር አለበት ሲሉ አመልክተዋል።rnrnከአምስት ወራት በፊት ከተከሰከሰው ተመሳሳይ የኢንዶኔዢያ አውሮፕላን በኋላ በኢትዮጵያ አውሮፕላን ላይ አደጋው ሲደገም ቦይንግ 737 ማክስ የተባለው አይነት ስሪት ያላቸው አውሮፕላኖች በሙሉ ከበረራ ታግደዋል።rnrnከሁለት ሳምንት በፊት በተከሰከሰው አውሮፕላን ውስጥ የነበሩት 157 መንገደኞች በሙሉ በአዳጋው ህይወታቸው ማለፉ ይታወሳል።rnrnአውሮፕላን አምራቹ ቦይንግ በቀረበበት ክስ ላይ እስካሁን ምላሽ አልሰጠም።rnrnረቡዕ እለት ቦይንግ ከአደጋዎቹ ጋር ግንኙነት አለው የተባለው በአውሮፕላኑ መቆጣጠሪያ ላይ ያለው ችግር መፍትሄ እንደተበጀለት እና የሶፍትዌር ማሻሻያ እንዳደረገ ይታወሳል ።rnrn 

More in Economy