ቦይንግ ከኢትዮጵያ አየር መንገዱ አደጋ ጋር በተያያዘ እየተከሰሰ ነውrnrnበኢትዮጵያ አየር መንገዱ አደጋ ህይወቱን ያጣ አንድ ግለሰብ ቤተሰቦች በአውሮፕላኑ አምራች ኩባንያ ቦይንግ ላይ በአሜሪካ የፌደራል ፍርድ ቤት ክስ መመስረታቸው ተሰምቷል።rnrnበአደጋው ህይወቱ ያለፈው ጃክሰን ሙሶኒ የሚባል ሩዋንዳዊ ግለሰብ ዘመዶች ናቸው በቦይንግ ላይ ክሱን የመሰረቱት፡፡rnrnየግለሰቡ ቤተሰቦች በክሳቸው ላይ አደጋው የደረሰበት ቦይንግ 737 ማክስ ኤት አውሮፕላን በአውቶማቲክ የበረራ መቆጣጠሪያ ሥርዓቱ ላይ የዲዛይን ችግር አለበት ሲሉ አመልክተዋል።rnrnከአምስት ወራት በፊት ከተከሰከሰው ተመሳሳይ የኢንዶኔዢያ አውሮፕላን በኋላ በኢትዮጵያ አውሮፕላን ላይ አደጋው ሲደገም ቦይንግ 737 ማክስ የተባለው አይነት ስሪት ያላቸው አውሮፕላኖች በሙሉ ከበረራ ታግደዋል።rnrnከሁለት ሳምንት በፊት በተከሰከሰው አውሮፕላን ውስጥ የነበሩት 157 መንገደኞች በሙሉ በአዳጋው ህይወታቸው ማለፉ ይታወሳል።rnrnአውሮፕላን አምራቹ ቦይንግ በቀረበበት ክስ ላይ እስካሁን ምላሽ አልሰጠም።rnrnረቡዕ እለት ቦይንግ ከአደጋዎቹ ጋር ግንኙነት አለው የተባለው በአውሮፕላኑ መቆጣጠሪያ ላይ ያለው ችግር መፍትሄ እንደተበጀለት እና የሶፍትዌር ማሻሻያ እንዳደረገ ይታወሳል ።rnrn
← NewsEconomy
Economy
Economy
Economy
ቦይንግ ከኢትዮጵያ አየር መንገዱ አደጋ ጋር በተያያዘ እየተከሰሰ ነው
Arts TV · ኤፕሪ 1 2019

More in Economy
Economyኢትዮጵያ ባለፉት አስር ወራት ከዓለም አቀፍ የፋይናንስ ተቋማት እና መንግስታት የ4.7 ቢሊዮን ዶላር የልማት ድጋፍ እንዳገኘች የገንዘብ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡
ጁን 6 2019
Economyበኮንትሮባንድ የሚሳተፉ አካላት አስተማሪ እርምጃ ሊወሰድባቸው ይገባል ተባለ፡፡
ሜይ 10 2019
ARTS
Economyከ37.4 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት ኮንትሮባንድ ማዕድናት ባለፉት ዘጠኝ መያዙን የገቢዎች ሚኒስቴር አስታወቀ ፡፡
ሜይ 7 2019
Economyየንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ለማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ ልዩ ትኩረት መስጠቱን ገለጸ፡፡
ሜይ 7 2019

