Arts TVArts TV
← NewsEconomy

በደሴና ድሬዳዋ አካባቢዎች ከአንድ ሚሊዮን ብር በላይ ግምታዊ ዋጋ ያላቸው የኮንትሮባንድ ዕቃዎችና ሺሻ በቁጥጥር ስር መዋሉን የገቢዎች ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡

Arts TV · ሜይ 3 2019

በደሴና ድሬዳዋ አካባቢዎች ከአንድ ሚሊዮን ብር በላይ ግምታዊ ዋጋ ያላቸው የኮንትሮባንድ ዕቃዎችና ሺሻ በቁጥጥር ስር መዋሉን የገቢዎች ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡

በደሴና ድሬዳዋ አካባቢዎች ከአንድ ሚሊዮን ብር በላይ ግምታዊ ዋጋ ያላቸው የኮንትሮባንድ ዕቃዎችና ሺሻ በቁጥጥር ስር መዋሉን የገቢዎች ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡rnrnሚኒስቴሩ የያዝኳቸዉ እቃዎች በድምሩ ከ1,073,021 ብር በላይ የሚገመቱ  ናቸዉ ብሏል፡፡rnrnከነዚህ ዉስጥ ግምታዊ ዋጋው 572,481 ብር የሚደርስ ኮንትሮባድ ሲጋራና ምስር ወደ ድሬዳዋ ከተማ ለማስገባት ሲሞከር የተያዘ ሲሆን፤ ኮንትሮባንዲስቶቹ ተኩስ በመክፈት የኮንትሮባድ ዕቃዎቹን ለማሳለፍ ሙከራ አድርገዉም  ነበር ተብሏል፡፡rnrnበተመሳሳይ መስመር 350 ሺህ ብር የሚጠጋ እርጥብ ጫት በህገ-ወጥ መንገድ ከሀገር ለማስወጣት ሲሞከር በጉምሩክ ሰራተኞችና በመከላከያ ሰራዊት የጋራ ጥረት በቁጥጥር ስር ውሏል፡፡rnrnግምታዊ ዋጋው 316,200 የሆነ የምግብ ዘይት በኤፍኤስ አር ተሽከርካሪ በአማራ ክልል በጉባ ላፍቶ ወረዳ ሀራ ተብሎ የሚጠራ ቦታ በክልሉ ፖሊስ አባላት የተያዘዉም በዚህ ሳምንት ነዉ፡፡rnrnሸዋሮቢት አካባቢ በሀሰተኛ ደረሰኝ 34,340 ብር የሚገመት ሽቶ ሲያዘዋውር የነበረ ግለሰብ እና  ደሴ ከተማ ውስጥም 719 ስቴካ ሺሻ መያዛቸዉንም ሰምተናል፡፡rnrnምንጭ ፤-ገቢዎች ሚኒስቴር

More in Economy