ሁለተኛው ኢትዮ ኪድስ የልጆች አዉደ ርዕይ በመኮንኖች ክበብ ተካሄደ፡፡rnrnለህጻናትና ታዳጊዎች የሚሆኑ ምርትና አገልግሎቶች ብቻ የቀረቡበትን አዉደ ርዕይ በርካታ ህጻናት ከወላጆቻቸው ጋር በመሆን ጎብኝተውታል፡፡rnrnለህጻናትና ታዳጊዎች ታስቦ የተዘጋጀዉ አዉደ ርዕይ በመሆኑ የተለያዩ የህጻናት አልባሳት፣ መጻህፍት፣ ሲዲዎችና ዲቪዲ እንዲሁም የመጫወቻ ቁሳቁሶች በስፋት የቀረቡበት ነበር፡፡rnrnበተጨማሪም አውደ ርዕዩን ለሚጎበኙ ህጻናት የተለያዩ የመዝናኛ አማራጮችም የቀረቡ ሲሆን የተለያዩ የህጻናት መጫወቻዎች እንዲሁም የሰርከስ ትርኢት እና የህጻናት ሙዚቃዎች ቀርበዋል፡፡rnrnበአውደ ርዕዩ ከህጻናት ጋር የተያያዙ ምርትና አገልግሎቶች ያሏቸው አምራቾች ፣አከፋፋዮች እና በችርቻሮ ንግድ ላይ የተሰማሩ ድርጅቶች የተሳተፉ ሲሆን ፤በህጻናት ልዩ ቁጠባ ላይ የተሰማሩ ባንኮችና የመድህን ድርጅቶች አገልግሎታቸውን አስተዋውቀዋል፡፡rnrnከህጻናት ጋር የተያያዙ ስራዎችን የሚሰሩ መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች የሚሰጡዋቸውን አገልግሎች አስመልክቶ የግንዛቤ ማስጨበጫ እና የማስተዋወቅ ስራ ሰርተዋል፡፡rnrnኢትዮ ኪድስ የልጆች አውደ ርዕይ ወላጆች ከልጆቻቸው ጋር በመሆን እየተዝናኑ የተለያዩ ምርቶችን በአንድ ቦታ የሚሸምቱበትና ድርጅቶችም በህጻናት ዙሪያ የሚሰጧቸውን አገልግሎቶች ለማስተዋወቅ ሰፊ እድል እንዲያገኙ የታለመ መሆኑን አዘጋጆቹ ነግረውናል፡፡rnrn rnrn






