68ኛ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ዉሳኔ አሳለፈrnrnየሚኒስትሮች ምክር ቤት ባካሄደው 68ኛ መደበኛ ስብስባ በተለያየ ጉዳዩች ላይ የተወያየ ሲሆን ፤ ከዚህ በፊት ወጥቶ በነበረው የፀረ ሽብርተኝነት አዋጅ በይዘት እና በአፈፃፀም ክፍተቶች የነበሩበት በመሆኑ ጠቅላይ አቃቤ ህግ የሌሎች ሀገራትን አለም አቀፍ ነበራዊ ሁኔታ ያገነዘበ አዋጅ አዘጋጅቶ ለሚነስትሮች ምክር ቤት ውሳኔ አቅርቧል፡፡rnrnምክርቤቱም በቀረበው ረቂቅ አዋጅ ላይ በዝርዝር ከተወያየ በኃላ ማሻሻያዎችን በመጨመር ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፍ መወሰኑን የጠቅላይ ሚኒስቴር ፅህፈት ቤት አስታውቋል፡፡rnrnበሌላ በኩል የተጨማሪ እሴት ታክስ አዋጅን ለማሻሻል ተዘጋጅቶ በቀረበ ረቂቅ አዋጅ ላይ የአለም አቀፍ ምርጥ ተሞክሮን ከግምት ውስጥ በማስገባት የአዋጁን አፈፃፀም በአዲስ አዋጅ መተካት አስፈላጊ በመሆኑ ፤ችግሩን ለመፍታት የገቢዎች ሚኒስቴር እና የገንዘብ ሚኒስቴር የተጨማሪ እሴት ታክስን አዋጅን ለማሻሻል ረቂቅ አዋጅ አዘጋጅተው ለሚኒስትሮች ምክርቤት ውሰኔ አቅርበዋል፡፡rnrnምክርቤቱም በቀረበው ረቂቅ አዋጅ ላይ ከተወያየ በኃላ አንዳንድ ማስተካከያዎችን በመጨመር ለህዝብ ተወካዮች ምክርቤት እንዲተላለፍ መወሰኑ ተነግሯል፡፡rnrnምክርቤቱ በቀረቡ ሶስት ከፍተኛ ደረጃ የመአድን ማምረት ስምምነት ፍቃዶች ላይ በዝርዝር ከተወያየ በኋላ ስምምነቶቹ በስራ ላይ እንዲውሉ ወስኗል፡፡





