ትራምፕ ስደተኞችን ችሎታ እና እድሜ ላይ ባተኮሩ መስፈርቶች እንቀበላን አሉ፡፡rnrnበስደተኞች ጉዳይ በብጥቅየሚተቹት የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ሀገራቸው ስደተኞችን የምትቀበልበት አዲስ ፖሊሲ ለማውጣት አቅደዋል፡፡rnrnበዚህም መሰረት ወደ አሜሪካ ለመግባት አንዱ መለኪያ ወጣትነት እንደሆነ ከዋይት ሀውስ የወጣው መረጃ ያሳያል፡፡rnrnቢቢሲ እንደዘገበው ወጣት መሆን በራሱ ግን ብቸኛ መስፈርት አይደለም፡፡ በተጨማሪም በትምህርታቸው የገፉ እና እንግሊዘኛን አቀላጥፈው የሚናገሩ ሰራተኞች አሜሪካ ገብተው እንዲሰሩ ይበረታታሉ በአዲሱ የኢሚግሬሽን ፖሊሲ፡፡rnrnትራምፕ ይህን ትልቅ ለውጥ የምናደርገው ወደ ሀገራችን ገብተው በእውቀት እና በክሎታቸው ውጤታማ ስራ የሚሰሩ ሰዎችን ቁጥር ለማብዛት ነው ብለዋል፡፡rnrnበፕሬዝዳንቱ የቀረበው አዲሱ የኢሚግሬሽን ፖሊሲ ተግባራዊ ከሆነ ወደ አሜሪካ የሚገቡ ስደተኞች ከትምህርት እና ከእንግለዝኛ ችሎታ በተጨማሪ የሲቪክስ ፈተና ወስደው ማለፍ ይጠበቅባቸዋል፡፡rnrnአዲሱ የትራምፕ እቅድ የሪፓብሊካን ፓርቲ ተወካይ ከሆኑት የምክር ቤት አባላት ተቃውሞ ቀርቦበታል፡፡rnrnለተቃውሟቸው አንዱ ምክንያት አዲሱ የፖሊሲ እቅድ አሜሪካ የሚገኙ 11 ሚሊዮን ሰነድ የሌላቸው ስደተኞችን አያካትትም የሚል ነው፡፡rnrnመንገሻ ዓለሙ





