Arts TVArts TV
← NewsSport

48ኛው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ዛሬ ይጀመራል

Arts TV · ሜይ 7 2019

48ኛው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ዛሬ ይጀመራል

<strong>ከ1963 ጀምሮ በየዓመቱ ሲካሄድ የነበረው ይህ ውድድር ዘንድሮ ለ48ኛ ጊዜ በአዲስ አበባ ስታዲየም ከሚያዚያ 29- ግንቦት 4/2011 ዓ/ም በ36 ክለቦችና ተቋማት መካከል ሲደረግ በአጠቃላይ 1376 አትሌቶች ይሳተፉበታል ተብሏል፡፡ </strong>rnrn<strong>የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ሁሉንም የአትሌቲክስ የውድድር ተግባራት በመካተት የሚካሄድ ይሆናል፡፡  </strong>rnrn<strong>የውድድሩ ዓላማ በአገር ውስጥ የውድድር ዕድል መፍጠር ፤ በክልሎች፣ ከተማ አስተዳደሮችና ክለቦች እንዲሁም ተቋማት መካከል የአትሌቲክስ ፉክክር መፍጠር፣ ለብሔራዊ ቡድን አትሌቶች ለመምረጥ እና ለዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ሚኒማ ሊያሟሉ የሚችሉ አትሌቶችን በዕጩነት ለመምረጥ የሚል ነው፡፡</strong>rnrn<strong>የውድድሩ አሸናፊ ለሚሆኑ አትሌቶች፣ ከአንዴ በላይ የወርቅ ሜዳሊያ ለሚያስመዘግቡ እና በቡድን ውጤት ለሚያስመዝግቡ አትሌቶች አንዲሁም ክብረወሰን ለሚያሻሽሉ አትሌቶች የገንዘብ ሽልማት ይኖራል ተብሏል፡፡</strong>rnrn<strong>ከ2.1 ሚሊየን ብር በላይ በጀት የተያዘለት ይህ ሻምፒዮና አስፈላጊው ቅድመ ዝግጅት እንደተደረገ ተገልጧል፡፡   </strong>

More in Sport