<strong>የቅዱስ ጊዮርጊስ ክለብ ዋና አሰልጣኝ የሆኑት እንግሊዛዊው ስቴዋርት ሃል ስራቸውን በገዛ ፈቃዳቸው የለቀቁ መሆኑን ትናንት ለስፖርት ማህበሩ በፃፉት ድብዳቤ አሳውቀዋል።</strong>rnrn<strong>የቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ማህበር ስራ አመራር ቦርድ ትናንት ከሰዓት ባካሄደው አስቸኳይ ስብሰባ አሰልጣኙ በራሳቸው ፈቃድ የለቀቁበትን ደብዳቤ ተመልክቶ ጥያቂያቸውን ተቀበሎታል፡፡ </strong>rnrn<strong>አሰልጣኙ የቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ማህበር ሥራ አመራር ቦርድ ላደረገላቸው ትብብር ምስጋና አቅርበዋል፡፡ </strong>rnrn<strong>ስራ አመራር ቦርዱም፤ አሰልጣኙ በክለቡ ቆይታቸው ወቅት ላከናወኗዋቸው ተግባራት አመስግኖ ቀጣይ ጨዋታዎችን ምክትል አሰልጣኝ ዘሪሁን ሸንገታ ዋና አሰልጣኝ ሆነው እንዲሰሩ ሰይሟል ሲል የክለቡ ይፋዊ የፌስቡክ ገፅ አስታውቋል፡፡</strong>rnrn<strong>በዘንድሮው የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ቅዱስ ጊዮርጊስ እስካሁን በተደረጉ የ24 ሳምንታት ጉዞ አስሩን በድል ሲወጣ፣ በስምንቱ አቻ ተለያይቶ በአምስት ጨዋታዎች ላይ ሸንፈት ገጥሞታል፡፡ </strong>rnrn<strong>ሊጉ ሊጠናቀቅ የስድስት ሳምንታት እድሜ የቀሩት ሲሆን ጊዮርጊስ 39 ነጥቦችን ሰብስቦ አራተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል፡፡</strong>
← NewsSport
Sport
Sport
Sport
Sport
ጊዮርጊስ እና አሰልጣኝ ስቴዋርት ሃል በይፋ ተለያይተዋል፡፡
Arts TV · ሜይ 15 2019

More in Sport
Sportበኮፓ አሜሪካ ግማሽ ፍፃሜ ብራዚል ከአርጀንቲና ዛሬ ሌሊት ተጠባቂ ጨዋታ ያደርጋሉ፡፡
ጁላይ 2 2019
Sportበሴቶች የዓለም ዋንጫ ግማሽ ፍፃሜ እንግሊዝ ከአሜሪካ የሚያደርጉት የዛሬ ምሽት ጨዋታ ይጠበቃል፡፡
ጁላይ 2 2019
Sportየወጋገን ናትና የ10 ኪ.ሜ የጎዳና ላይ ሩጫ ውድድር ከሰኔ 30 ወደ ሐምሌ 7 እንደተራዘመ ተገለፀ፡፡
ጁላይ 1 2019
Sportበኮፓ አሜሪካ ብራዚል ግማሽ ፍፃሜውን ስትቀላቀል፤ አርጀንቲና ዛሬ ምሽት ተጠባቂ ጨዋታ ይኖራታል፡፡
ጁን 28 2019

