<strong>በሚቀጥለው የእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ የውድድር ዓመት የሚሳተፍ ሶስተኛውን ክለብ ለመለየት ዛሬ አመሻሽ 11፡00 ሰዓት በግዙፉ ዌምብሌይ ስታዲየም ይደረጋል፡፡</strong>rnrn<strong>ተፋላሚዎቹ ደግሞ አስቶን ቪላ እና ደርቢ ካውንቲ ናቸው፤ በቼልሲ አብረው ስኬትን የተቋደሱት ጆን ቴሪ እና ፍራንክ ላምፓርድ ደግሞ በአሰልጣኝነት የተለያዩ ቡድኖችን ይዘው ተፋጥጠዋል፡፡</strong>rnrn<strong>የቪላ አሰልጣኝ ዲን ስሚዝ ምክትል ሆኖ እያገገለገለ የሚገኘው ቴሪ ሲሆን ላምፓርድ ደርቢን በዋና አሰልጣኝነት በተረከበበት ዓመት ወደ ሊጉ ሊያሻግረው ጫፍ ላይ ደርሷል፡፡</strong>rnrn<strong>በደርሶ መልስ ጨዋታዎች አስቶን ቪላ ዌስት ብሮም አልቢዮንን እንዲሁም ደርቢ ካውንቲ የማርሴሎ ቤልሳውን ሊድስ ዩናይትድ በመጣል ነበር ለዚህ የፍፃሜ ጨዋታ መብቃት የቻሉት፡፡</strong>rnrn<strong>የጨዋታው አሸናፊ ከኖርዊች እና ሼፊልድ ዩናይትድ በመከተል፤ 170 ሚሊዬን ፓውንድ ጋር ሶስተኛው 2019/20 የእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ ተሳታፊ ቡድን መሆኑን ያረጋግጣል፡፡</strong>rnrn<strong>በቻምፒዮንሽፑ የውድድር ዓመት ቪላ በፍራንክ ላምፓርድ ቡድን ላይ ሁለቱን ጨዋታ (በ3 ለ 0 እና 4 ለ 0) ድል በማድረግ የበላይነት አለው፡፡</strong>rnrn<strong> </strong>
← NewsSport
Sport
Sport
Sport
Sport
የ170 ሚሊዬን ፓውንድ ዋጋ ያለው ጨዋታ ዛሬ ይደረጋል፡፡
Arts TV · ሜይ 27 2019

More in Sport
Sportበኮፓ አሜሪካ ግማሽ ፍፃሜ ብራዚል ከአርጀንቲና ዛሬ ሌሊት ተጠባቂ ጨዋታ ያደርጋሉ፡፡
ጁላይ 2 2019
Sportበሴቶች የዓለም ዋንጫ ግማሽ ፍፃሜ እንግሊዝ ከአሜሪካ የሚያደርጉት የዛሬ ምሽት ጨዋታ ይጠበቃል፡፡
ጁላይ 2 2019
Sportየወጋገን ናትና የ10 ኪ.ሜ የጎዳና ላይ ሩጫ ውድድር ከሰኔ 30 ወደ ሐምሌ 7 እንደተራዘመ ተገለፀ፡፡
ጁላይ 1 2019
Sportበኮፓ አሜሪካ ብራዚል ግማሽ ፍፃሜውን ስትቀላቀል፤ አርጀንቲና ዛሬ ምሽት ተጠባቂ ጨዋታ ይኖራታል፡፡
ጁን 28 2019

