Arts TVArts TV
← NewsSport

የ170 ሚሊዬን ፓውንድ ዋጋ ያለው ጨዋታ ዛሬ ይደረጋል፡፡

Arts TV · ሜይ 27 2019

የ170 ሚሊዬን ፓውንድ ዋጋ ያለው ጨዋታ ዛሬ ይደረጋል፡፡

<strong>በሚቀጥለው የእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ የውድድር ዓመት የሚሳተፍ ሶስተኛውን ክለብ ለመለየት ዛሬ አመሻሽ 11፡00 ሰዓት በግዙፉ ዌምብሌይ ስታዲየም ይደረጋል፡፡</strong>rnrn<strong>ተፋላሚዎቹ ደግሞ አስቶን ቪላ እና ደርቢ ካውንቲ ናቸው፤ በቼልሲ አብረው ስኬትን የተቋደሱት ጆን ቴሪ እና ፍራንክ ላምፓርድ ደግሞ በአሰልጣኝነት የተለያዩ ቡድኖችን ይዘው ተፋጥጠዋል፡፡</strong>rnrn<strong>የቪላ አሰልጣኝ ዲን ስሚዝ ምክትል ሆኖ እያገገለገለ የሚገኘው ቴሪ ሲሆን ላምፓርድ ደርቢን በዋና አሰልጣኝነት በተረከበበት ዓመት ወደ ሊጉ ሊያሻግረው ጫፍ ላይ ደርሷል፡፡</strong>rnrn<strong>በደርሶ መልስ ጨዋታዎች አስቶን ቪላ ዌስት ብሮም አልቢዮንን እንዲሁም ደርቢ ካውንቲ የማርሴሎ ቤልሳውን ሊድስ ዩናይትድ በመጣል ነበር ለዚህ የፍፃሜ ጨዋታ መብቃት የቻሉት፡፡</strong>rnrn<strong>የጨዋታው አሸናፊ ከኖርዊች እና ሼፊልድ ዩናይትድ በመከተል፤ 170 ሚሊዬን ፓውንድ ጋር ሶስተኛው 2019/20 የእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ ተሳታፊ ቡድን መሆኑን ያረጋግጣል፡፡</strong>rnrn<strong>በቻምፒዮንሽፑ የውድድር ዓመት ቪላ በፍራንክ ላምፓርድ ቡድን ላይ ሁለቱን ጨዋታ (በ3 ለ 0 እና 4 ለ 0) ድል በማድረግ የበላይነት አለው፡፡</strong>rnrn<strong>  </strong>

More in Sport