Arts TVArts TV
← NewsSport

የኮፓ ዴል ሬይ የፍፃሜ ጨዋታ ነገ ምሽት ይደረጋል፡፡

Arts TV · ሜይ 24 2019

የኮፓ ዴል ሬይ የፍፃሜ ጨዋታ ነገ ምሽት ይደረጋል፡፡

<strong>117ኛው የስፔን ኮፓ ዴል ሬይ ወይንም የስፔን ንጉስ ዋንጫ የፍፃሜ ጨዋታ በነገው ዕለት ምሽት 4፡00 ሰዓት ላይ ይደረጋል፡፡</strong>rnrn<strong>ግጥሚያው በባርሴሎና እና ቫሌንሲያ መካከል ሲቪያ ውስጥ በሚገኘው በሪያል ቤትስ ቤኒቶ ቪያማሪን ስታዲየም ይደረጋል፡፡</strong>rnrn<strong>በአሰልጣኝ ኤርኔስቶ ቫልቬርዴ የሚመራው የካታላኑ ቡድን በግማሽ ፍፃሜው ተቀናቃኙን ሪያል ማድሪድ በደርሶ መልስ 4 ለ 1 ድል በማድረግ ለተከታታይ ስድስተኛ የፍፃሜ ጨዋታ ሲበቃ የተመሰረተበትን መቶኛ ዓመት እያከበረ የሚገኘው የማርሴሊኖው ቡድን ቫሌንሲያ ደግሞ ሪያል ቤቲስን 3 ለ 2 ማሸነፍ ችሏል፡፡   </strong>rnrn<strong>ባርሳ 41ኛውን የፍፃሜ ጨዋታ የሚያደርግ ሲሆን ለአምስተኛ ተከታታይ ድሉ፤ በአጠቃላይ ደግሞ ለ31ኛ የንጉስ ዋንጫ ድሉ ይጫወታል፡፡ ቫሌንሲያ እስካሁን 7 ጊዜ ዋንጫውን ከፍ ያደረገ ሲሆን ለስምንተኛ ድሉ ይፋለማል፡፡</strong>rnrn<strong>ቫሌንሲያ ዋንጫውን ለመጨረሻ ጊዜ ያነሳው በ2008 ቪንሴንቴ ካልዴሮን ላይ ሄታፌን 3 ለ 1 በማሸነፍ ነበር፡፡</strong>rnrn<strong>ጨዋታው በአርቢትር አልቤርቶ ኡንዲያኖ ማዬንኮ ይመራል፡፡</strong>

More in Sport