<strong>ተጠባቂው የሸገር ደርቢ በዚህ ሳምንት መርሀግብር የሚከናወን ሲሆን በዕለተ ሰንበት 10፡00 ሰዓት ላይ በኢትዮጵያ ቡና እና ቅዱስ ጊዮርጊስ መካከል ይደረጋል፡፡</strong>rnrn<strong>የበርካታ ደጋፊዎች ባለቤቶች ሁለቱ የአዲስ አበባ ክለቦች የዘንድሮው የሊጉ ውድድር የልብ ደጋፊዎቻቸውን ጭምር ያላስደሰተ ጉዞ እያደረጉ ይገኛሉ፡፡</strong>rnrn<strong>በመጀመሪያው ዙር ያለግብ በአቻ ውጤት መለያየታቸው ይታወሳል፤ አሁን በሊጉ የደረጃ ሰንጠራዥ ፈረሰኞቹ በ37 ነጥብ እና 13 ንፁህ ጎሎች ሶስተኛ ደረጃ ላይ ሲገኙ፤ ቡናማዎቹ በ32 ነጥብ 8ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጠዋል፡፡ </strong>rnrn<strong>ቅዳሜ ዕለት ሶስት ግጥሚያዎች ሲከናወኑ፤ ሁለቱ በክልል ስታዲየሞች ላይ በተመሳሳይ 9፡00 ይደረጋሉ፡፡ </strong>rnrn<strong>የጎንደሩ ፋሲል ከነማ ወደ ትግራይ ክልል በመጓዝ መቐለ ላይ በግዙፉ ስታዲየም የወራጅ ቀጠና ግርጌ ላይ የሚገኘውን ደደቢት የሚገጥም ይሆናል፡፡ </strong>rnrn<strong>ሌላኛው ወራጅ ቀጠና ላይ የሚገኘው ቡድን ደቡብ ፖሊስ ሀዋሳ ላይ አዳማ ከተማን ያስተናግዳል፡፡</strong>rnrn<strong>አሰልጣኝ ጳውሎስ ጌታቸው (ማንጎ)ን ወደ ስራቸው እንዲመለሱ ያደረገው ባህር ዳር ከነማ ወደ አዲስ አበባ መጥቶ ከመከላከያ ጋር ይጫወታል፡፡ የጣና ሞገዶቹ ከ20ኛ ሳምንት የሊጉ መርሀግብር እዚሁ ስታዲየም በኢትዮያ ቡና 5 ለ 0 መረታታቸው ይታወሳል፡፡ </strong>rnrn<strong>እሁድና ሰኞ የ22ኛ ሳምንት የፕሪምየር ሊጉ ጨዋታዎች ሲቀጥሉ በዕለተ ሰንበት ከሸገር ደርቢ በተጨማሪ ሶስት ግጥሚያዎች በክልል ስታዲየሞች እንዲሁም ሰኞ አንድ የሳምንቱ የማሳረጊያ ግጥሚያ በተመሳሳይ 9፡00 ሰዓት ይደረጋሉ፡</strong>rnrn<strong>የደቡቡ ክለብ ወላይታ ድቻ ወደ ምስራቅ አቅንቶ፤ ከድሬዳዋ ከነማ ጋር ይፋለማል፡፡ </strong>rnrn<strong>የሊጉ አናት ላይ የተቀመጠው መቐለ 70 እንደርታ በትግራይ ስታዲየም ከስሑል ሽረ ጋር ትልቅ ትንቅንቅ ያለበትን የትግራይ ደርቢ ጨዋታ ያደርጋል፡፡ መቐለ በሊጉ መሪነት ለመግፋት፣ ሽረ ከወራጅ ቀጠና ለመውጣት የሚደረግ ግጥሚያ መሆኑ ጨዋታው ይጠበቃል፡፡</strong>rnrn<strong>ሀዋሳ ከተማ በደቡብ ደርቢ ከሲዳማ ቡና ጋር ጥሩ ጨዋታ ያደርጋሉ፡፡ ሰኞ ጅማ አባ ጅፋር በትግራይ ስታዲየም ወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲን ይጎበኛል፡፡</strong>rnrn<strong>በኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ የ21 ሳምንታት ጉዞ መቐለ 70 እንደርታ በ45 ነጥቦች ቀዳሚ ነው፤ ፋሲል ከነማ በአምስት ነጥብ አንሶ 40 ነጥብ ሰብስቦ 2ኛ ደረጃን ይዟል፤ ቅዱስ ጊዮርጊስ፣ ሲዳማ ቡና እና ጅማ አባ ጅፋር በተመሳሳይ 37 ነጥብ ባለቸው ንፁህ የግብ ክፍያ ከ3- 4 ያለውን ደረጃ ይዘዋል፡፡ </strong>
← NewsSport
Sport
Sport
Sport
Sport
የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ የ23ኛ ሳምንት ጨዋታዎች በመጪዎቹ የሳምንቱ የመጨረሻ ቀናት ይከናወናሉ
Arts TV · ሜይ 3 2019

More in Sport
Sportበኮፓ አሜሪካ ግማሽ ፍፃሜ ብራዚል ከአርጀንቲና ዛሬ ሌሊት ተጠባቂ ጨዋታ ያደርጋሉ፡፡
ጁላይ 2 2019
Sportበሴቶች የዓለም ዋንጫ ግማሽ ፍፃሜ እንግሊዝ ከአሜሪካ የሚያደርጉት የዛሬ ምሽት ጨዋታ ይጠበቃል፡፡
ጁላይ 2 2019
Sportየወጋገን ናትና የ10 ኪ.ሜ የጎዳና ላይ ሩጫ ውድድር ከሰኔ 30 ወደ ሐምሌ 7 እንደተራዘመ ተገለፀ፡፡
ጁላይ 1 2019
Sportበኮፓ አሜሪካ ብራዚል ግማሽ ፍፃሜውን ስትቀላቀል፤ አርጀንቲና ዛሬ ምሽት ተጠባቂ ጨዋታ ይኖራታል፡፡
ጁን 28 2019

