<strong>በተለያዩ ክለቦች የተጫወተው ሞሮኳዊው ኢንተርናሽናል ማሩዋን ቻማክ ላለፉት </strong>rnrn<strong>ሁለት ዓመት ከግማሽ ሳይጫወት ከቆየ በኋላ በ35 ዓመቱ በይፋ እግር ኳስ መጫወት ማቆሙን አስታውቋል፡፡</strong>rnrn<strong>የቀድሞው የአርሰናል ተጫዋች በዌስት ሃም ዩናይትድ፣ ክሪስታል ፓላስ፣ ካርዲፍ ሲቲ እና የፈረንሳዩ ቦርዶ ተጫውቶ አሳልፏል፡፡</strong>rnrn<strong>ተጫዋቹ በ2016 የዌልሱን ካርዲፍ ከተሰናበተ በኋላ ያለምንም ክለብ ቆይታ አድርጓል፡፡</strong>rnrn<strong>ቻማክ ለቤን ስፖርትስ እንዳለው በእውነት ዛሬ ከእግር ኳስ መገለሌን አስታውቃለሁ ሲል ገልጧል፡፡</strong>rnrn<strong>በፈረንሳይ የተወለደው ቻማክ ስምንት ዓመታትን በቦርዶ በማሳለፍ፤ በ230 የሊጉ ጨዋታዎች ላይ 56 ጎሎችን በማስቆጠር፤ አንድ የሊግ አንድ እና የፈረንሳይ ሊግ ዋጫዎችን ማሳካት ችሏል፡፡</strong>rnrn<strong>በ2010 ወደ አርሰናል መጥቶ በሶስት የውድድር ዓመት ቆይታው፤ በ40 የፕሪምየር ሊግ ግጥሚያዎች ላይ ተሰልፎ ስምንት ጎሎችን ብቻ አስቆጥሯል፡፡</strong>rnrn<strong>ቻማክ በብሔራዊ ቡድን ደረጃ ለፈረንሳይ ከ19 ዓመት በታች ቢሰለፍም፤ ዋናውን የብሄራዊ ቡድን አገልግሎት ግን ለሞሮኮ ከ2003 ጀምሮ ሰጥቷል፡፡ ለሀገሩም በ68 ግጥሚያዎች 18 ግቦችን ማበርከት ችሏል፡፡ </strong>
← NewsSport
Sport
Sport
Sport
Sport
የቀድሞው የአርሰናል ተጫዋች ማሩዋን ቻማክ ጫማ ሰቅሏል፡፡
Arts TV · ሜይ 27 2019

More in Sport
Sportበኮፓ አሜሪካ ግማሽ ፍፃሜ ብራዚል ከአርጀንቲና ዛሬ ሌሊት ተጠባቂ ጨዋታ ያደርጋሉ፡፡
ጁላይ 2 2019
Sportበሴቶች የዓለም ዋንጫ ግማሽ ፍፃሜ እንግሊዝ ከአሜሪካ የሚያደርጉት የዛሬ ምሽት ጨዋታ ይጠበቃል፡፡
ጁላይ 2 2019
Sportየወጋገን ናትና የ10 ኪ.ሜ የጎዳና ላይ ሩጫ ውድድር ከሰኔ 30 ወደ ሐምሌ 7 እንደተራዘመ ተገለፀ፡፡
ጁላይ 1 2019
Sportበኮፓ አሜሪካ ብራዚል ግማሽ ፍፃሜውን ስትቀላቀል፤ አርጀንቲና ዛሬ ምሽት ተጠባቂ ጨዋታ ይኖራታል፡፡
ጁን 28 2019

