Arts TVArts TV
← NewsSport

የቀድሞው የአርሰናል ተጫዋች ማሩዋን ቻማክ ጫማ ሰቅሏል፡፡

Arts TV · ሜይ 27 2019

የቀድሞው የአርሰናል ተጫዋች ማሩዋን ቻማክ ጫማ ሰቅሏል፡፡

<strong>በተለያዩ ክለቦች የተጫወተው ሞሮኳዊው ኢንተርናሽናል ማሩዋን ቻማክ ላለፉት </strong>rnrn<strong>ሁለት ዓመት ከግማሽ ሳይጫወት ከቆየ በኋላ በ35 ዓመቱ በይፋ እግር ኳስ  መጫወት ማቆሙን አስታውቋል፡፡</strong>rnrn<strong>የቀድሞው የአርሰናል ተጫዋች በዌስት ሃም ዩናይትድ፣ ክሪስታል ፓላስ፣ ካርዲፍ ሲቲ እና የፈረንሳዩ ቦርዶ ተጫውቶ አሳልፏል፡፡</strong>rnrn<strong>ተጫዋቹ በ2016 የዌልሱን ካርዲፍ ከተሰናበተ በኋላ ያለምንም ክለብ ቆይታ አድርጓል፡፡</strong>rnrn<strong>ቻማክ ለቤን ስፖርትስ እንዳለው በእውነት ዛሬ ከእግር ኳስ መገለሌን አስታውቃለሁ ሲል ገልጧል፡፡</strong>rnrn<strong>በፈረንሳይ የተወለደው ቻማክ ስምንት ዓመታትን በቦርዶ በማሳለፍ፤ በ230 የሊጉ ጨዋታዎች ላይ 56 ጎሎችን በማስቆጠር፤ አንድ የሊግ አንድ እና የፈረንሳይ ሊግ ዋጫዎችን ማሳካት ችሏል፡፡</strong>rnrn<strong>በ2010 ወደ አርሰናል መጥቶ በሶስት የውድድር ዓመት ቆይታው፤ በ40 የፕሪምየር ሊግ ግጥሚያዎች ላይ ተሰልፎ ስምንት ጎሎችን ብቻ አስቆጥሯል፡፡</strong>rnrn<strong>ቻማክ በብሔራዊ ቡድን ደረጃ ለፈረንሳይ ከ19 ዓመት በታች ቢሰለፍም፤ ዋናውን የብሄራዊ ቡድን አገልግሎት ግን ለሞሮኮ ከ2003 ጀምሮ ሰጥቷል፡፡ ለሀገሩም በ68 ግጥሚያዎች 18 ግቦችን ማበርከት ችሏል፡፡    </strong>

More in Sport