Arts TVArts TV
← NewsSport

የሉሲዎቹ አሰልጣኝ ሰላም ዘርዓይ ለ25 ተጫዋቾች ጥሪ አደረገች::

Arts TV · ጁን 7 2019

የሉሲዎቹ አሰልጣኝ ሰላም ዘርዓይ ለ25 ተጫዋቾች ጥሪ አደረገች::

<strong>የኢትዮጵያ ሴቶች ብሔራዊ ቡድን (ሉሲዎቹ) ከጋምቢያ አቻቸው ጋር ላለባቸው የወዳጅነት ጨዋታ የብሔራዊ ቡድኑ አሰልጣኝ ሰላም ዘርዓይ ለ25 ተጫዋቾች ጥሪ ማድረጓን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ድረ ገፅ ይፋ አድርጓል።</strong>rnrn<strong>በጋምቢያ ባካው ከተማ ላይ ሰኔ 8 እና 11 ሉሲዎቹ ሁለት የወዳጅነት ጨዋታቸውን ያከናውናሉ። ለዚህም እንዲረዳት አሰልጣኝ ሰላም ዘርዓይ ለተጫዋቾች ጥሪ አድርጋለች።</strong>rnrn<strong>ከግብ ጠባቂዎች</strong>rnrn<strong>የጥረት ኮርፖሬቷ ታሪኳ በርገና፤ የሀዋሳ ከተማው አባይነሽ ኤርቄሎ፤ የመከላከያዋ ማርታ በቀለ ጥሪ ደርሷቸዋል፡፡ </strong>rnrn<strong>በተከላካይ መስመር </strong>rnrn<strong>መስከረም ኮንካ፣ ናርዶስ ጌትነት፣ እጸገነት ብዙነህ፣ ነጻነት ጸጋዬ ከአዳማ ከተማ፤ ገነሜ ወርቁ እና ብዙአየሁ ታደሰ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፤ መሰሉ አበራ ከ መከላከያ እና የሐዋሳ ከተማዋ ቅድስት ዘለቀ ተመርጠዋል፡፡</strong>rnrn<strong>ከአማካኝ ተጫዋቾች ደግሞ ህይወት ደንጊሶ እና ብርቱካን ገ/ክርስቶስ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፤ ከመከላከያ እመቤት አዲሱ እና አረጋሽ ካልሳ፤ አለምነሽ ገረመው ከኢትዮ ኤሌክትሪክ፤ ሰናይት ቦጋለ ከአዳማ ከተማ እንዲሁም ይመችሽ ዘውዴ ከድሬዳዋ ከተማ ተካትተዋል፡፡</strong>rnrn<strong>በአጥቂ ስፍራ </strong>rnrn<strong>ሎዛ አበራ፣ ገነት ሀይሉ፣ ሴናፍ ዋቁማ እና ሰርክአዲስ ጉታ ከአዳማ ከተማ፤ መዲና ጀማል እና ሔለን እሸቱ ከመከላከያ እና ምርቃት ፈለቀ ከሀዋሳ ከተማ ጥሪ ተደርጎላቸዋል ተብሏል፡፡</strong>rnrn<strong>ጥሪ የደረሳቸው እነዚህ ተጫዋቾች በነገው ዕለት ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ጽ/ቤት ሪፖርት እንዲያደርጉ ተብሏል።</strong>

More in Sport