በካሜሮን በታጣቂዎች ታፍነው የተወሰዱ 79 ተማሪዎች ተለቀቁr
አርትስ 29/02/2011
rበካሜሮን ሰሜናዊ ምስራቅ ግዛት ከሚገኝ አዳሪ ትምህርት ቤት ውስጥ በታጣቂዎች ታፍነው የተወሰዱ 79 ተማሪዎች መለቀቃቸው ተነገረ፡፡
rእስካሁን የትምህርት ቤቱን ርዕሰ መምህር ጨምሮ አንድ መምህርና ሾፌር አሁንም በእገታ ላይ ናቸው፡፡
rቢቢሲ እንደዘገበው የሀገሪቱ መንግስት ታጋቾችን ለማስለቀቅ በትናንትናው ዕለት በሄሊኮፕተር የታገዘ ፍለጋ ማድረግ ጀምሮ ነበር።
rነገር ግን የተለቀቁት 79 ተሪዎች በምን ሁኔታ ሊለቀቁ እንደበቁ የታወቀነገር የለም።





