ጉዳት የደረሰባቸዉን የአካል ክፍል የሚተኩ (የአካላዊ ተሃድሶ ህክምና በሁሉም መንግስት ጤና ተቋማት ሊሰጥ መሆኑን ጤና ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡rnrnቀደም ሲል በሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳዮች ሚኒስቴር ስር የነበሩ የአካላዊ ተሃድሶ ህክምና ተቋማት ሙሉ ለሙሉ ወደ ጤና ሚኒስቴር እንዲዛወሩ በተገባው ውል መሰረት የርክክብ ስራ እየተሰራ ነዉ፡፡rnrnየጤና ሚኒስቴር የክሊኒካል ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ አባስ ሀሰን በጉዳዩ ላይ በተደረገ ዉይይት ላይ እንደተናገሩት የጤና አገልግሎት እኩል ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ሁሉንም የህብረተሰብ ክፍሎች በተለይም የአካላዊ ህክምና አገልግሎት መካተት አለበት ብለዋል፡፡rnrnበየጤና ተቋማት የአካላዊ ተሃድሶ ህክምና ትኩረት ያልተሰጠው በመሆኑ ታካሚዎች ህክምናው ለመውሰድ ይቸገራሉ ተብሏል፡፡rnrnበአገር አቀፍ ደረጃ 11 የአካላዊ ተሃድሶ ህክምና እየሰጡ ያሉ ማዕከላት ሲኖሩ ህክምናዉን በሁሉም የመንግስት ሆስፒታሎችና ጤና ተቋማት ወጥ በሆነ መንገድ ለመስጠት አራት ምዕራፎች ያሉት መመሪያ ተዘጋጅቶ ወደ ስራ ተገብቷል፡፡rnrnበአገር አቀፍ ደረጃ በአካላዊ ተሃድሶ ህክምና የአለርት ሆስፒታል ጥሩ ተሞክሮ እንዳለዉ ከጤና ሚኒስቴር ሰምተናል፡፡
← NewsHealth
ጉዳት የደረሰባቸዉን የአካል ክፍል የሚተኩ (የአካላዊ ተሃድሶ ህክምና በሁሉም መንግስት ጤና ተቋማት ሊሰጥ መሆኑን ጤና ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡
Arts TV · ኤፕሪ 18 2019






