የኔፓል ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር በኢትዮጵያ ጉብኝት ሊያደረጉ ነዉ፡፡rnrnምክትል ጠቅይ ሚኒስተሩ ኡፔነድራ ያዳቫ እና የፓርላማ አባሎቻቸው ከጤና ሚኒስትር ጋር በመሆን ጉብኝታቸዉን በኦሮሚያ ክልል ያደርጋሉ ተብሏል፡፡rnrnበጉብኝታቸው ወቅት በክልሉ ያለውን የጤናው ዘርፍ አገልግሎት አስጣጥ ከጤና ቢሮ እስከ ጤና ኬላ ድረስ በመዝለቅና በመመልከት የልምድ ልውውጥ ለማድረግ ማቀዳቸው ተነግሯል፡፡rnrnጎበኝዎቹን የተቀበሉት የጤና ሚኒስትር ደኤታዋ ወ/ሮ ሰሀረላ አቡደላሂ እንደተናገሩት ሀገራችን በእናቶች ጤና፣ በወረዳ ትራንሰረፎርሜሽንና በጤና ኤክስቴንሽን ፕሮግራም እያስመዘገበች ያለችው ለውጥ አመርቂ መሆኑን ገልጸዋል፡፡rnrnይህንን ተሞክሮ ወደ ሀገራችሁ በመውሰድ እንደምትተገብሩትና ሀገራችንም ከኔፓል የምትማረው ብዙ ነገር እንዳለም እምነት አለን ብለዋል፡፡rnrnየጤና ሚኒስቴር እንደገለጸዉ በውይይቱም ወቅት የኢትዮጵያን የጤና አገልግሎት አሰጣጥና የጤና ስርአት አተገባበር አስመልክቶ ገለፃ ተደርጎላቸዋል ፡፡






