የመድሃኒት አያያዝ እና አገልግሎት አሰጣጥ ችግር በታየባቸው መድህኒት ቸርቻሪ ድርጅቶች ላይ ህጋዊ እርምጃ እየተወሰደ ነውrnrnበጉዳዩ ዙሪያ ጥናታዊ ፅሁፍ ቀርቦ ከመድሃኒት ቸርቻሪ ድርጅቶች ጋር የዉይይት መድረክ ለካሄዷል፡፡rnrnበመድረኩ ላይ የተገኙት የአዲስ አበባ ከተማ ምግብ መድሃኒት ጤና ክብካቤ አስተዳደርና ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ ጌታቸው ወረቴ እንደ ናሙና በተመረጡ የከተማችን 86 መድሃኒት ቸርቻሪ ድርጅቶች ላይ በተደረገባቸው ጥናት የመድህኒት አያያዝ፣ የአገልግሎት አሰጣጥና ምንጫቸው የማይታወቅ መድሃኒቶችን የመጠቀም ችግሮች መኖራቸውን ማረጋገጥ መቻላቸውን ተናግረዋል፡፡rnrnዋና ዳይሬክተሩ ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ለህብረተሰቡ ጥራቱና ደህንነቱ እና ፈዋሽነቱ የተጠበቀ የመድሃኒት አገልግሎት ተደራሽ በማያደርጉ መድሀኒት ቸርቻሪ ድርጅቶች ላይ ህጋዊ እርምጃ እየወሰደ መሆኑንና ይህም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቀዋል፡፡
← NewsHealth
የመድሃኒት አያያዝ እና አገልግሎት አሰጣጥ ችግር በታየባቸው መድህኒት ቸርቻሪ ድርጅቶች ላይ ህጋዊ እርምጃ እየተወሰደ ነው
Arts TV · ፌብ 5 2019






