የህክምና ጥራትን ማሻሻል የሀገርን ኢኮኖሚ ለማሳድግ ያግዛል ተባለ፡፡rnrnይህ የተባለዉ የኢፌዲሪ ጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ከኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ጋርrnrnበሀገር ውስጥ የሚገኙ የመድኃኒትና የህክምና መሳሪያዎች ማምረቻ ፋብሪካዎች የሚጠናከሩበትን መንገድ በመከሩበት ወቅት ነዉ፡፡rnrnየጤና ጥበቃ ሚኒስትር ዶክተር አሚር አማን እንዳሉት የሀገራችንን የህክምና ጥራት በማሻሻል ኢኮኖሚ ያችንን ማሳደግ ይቻላል ፡፡rnrnእንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር በ2016 በተደረገ ጥናት ኢትዮጵያ የህክምና መድኀኒቶችን እና የህክምና መሳሪያዎች ወደ ሀገር ውስጥ ለማስገባት 474 ሚሊዮን ዶላር አውጥታለች ተብሏል::rnrnበሀገር ውስጥ የሚገኙ የመድኃኒትና የህክምና መሳሪያዎች ማምረቻ ፋብሪካዎች ከተጠናከሩ ግን ሀገሪቱ ለህክምና መሳሪዎችና መድሀኒት ግዢ የምታወጣዉን ከፍተኛ የዉጭ ምንዛሪ ማስቀረት ያስችላል ፡፡rnrn rnrn rnrn






