የህክምና መሳሪያዎችን ከባክቴሪያ ነፃ የሚያደርግ መሳሪያ በኢትዮጵያ ሊመርት ነው፡፡rnrnመሳሪያው ጋዝን ብቻ በመጠቀም የህክምና መሳሪያዎችን ነጻ በማድረግ ለድጋሚ አገልግሎት ዝግጁ እንዲሆኑ የሚያደርግ ነው፡፡rnአሁን ጥቅም ላይ ያሉት መሳሪያዎች በህክምና ጣቢያዎች ውስጥ ተቀምጠው ውሃና መብራትን የሚጠቀሙ ናቸው፡፡rnአይ ኤም ጂ ኢንተርናሽናል ሜዲካል ግሩፕ በኢትዮጵ የሚያመርተዉ ተንቀሳቃሽ መሳሪያ ግን ውሃና መብራት የማይፈልግ ሲሆን በቀላሉ ከቦታ ቦታ በማንቀሳቀስ ጥቅም ላይ የሚውል ነው ተብሏል፡፡rnመሳሪያውን በኢትዮጵያ ለማምረት የሚያስችለዉን ስምምነት የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታው ዶክተር ሹመቴ ግዛው እና ከአይ ኤም ጂ ኢንተርናሽናል የህክምና ቡድን የአፍሪካ ዳይሬክተር ዶ/ር ትግስቱ አዳሙ ስምምነቱን ተፈራርመዋል፡፡rnተን ቀሳቃሽ መሳሪያዉ ከኪሚካል ኢንዱስትሪዎች ጋዝ በቀላሉ ማግኘት ስለሚቻል የግብዓት ችግር እንደማይኖር ተጠቁሟል፡፡rnማንኛውንም የህክምና መሳሪያዎችን ለድጋሚ ግልጋሎት ዝግጁ የሚያደርገው ይህ መሳሪያ የውሃና መብራት እጥረት ባለበት አካባቢ የሚሰጠውን ህክምና ለማገዝ ትልቅ ሚና ስለሚኖረው ወደ ምርት እንዲገባ አስፈላጊውን እገዛ እንደሚያደርግ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ገልጽዋል፡፡rnrn






