ኮንጎ በኢቦላ በሽታ 26 ዜጎቿን በአንድ ጀንበር አጣች፡፡rnrnየዲሞክራቲክ ሪፓብሊክ ኮንጎ የጤና ሚኒስቴር እንዳስታወቀው በሰሜናዊ የኪቩ ግዛት የተከሰተው የኢቦላ ቫረስ ትልቅ ስጋትን ፈጥሯል፡፡rnrnበሀገሪቱ ቫይረሱ ከተከሰተ አንስቶ በጠቅላላው 957 ሰዎች ህይዎታቸው ቢያልፍም በአንድ ቀን 26 ህሙማን ሲሞቱ ግን ከፍተኛ መደናገጥን አስከትሏል፡፡rnrnአጃንስ ፍራንስ ፕሬስ እንደዘገበው ህሙማኑን በሞያቸው ለመርዳት የተሰማሩ 33 የጤና ሞያተኞችም በቫይረሱ ተይዘዋል፡፡rnrnአሁን በኮንጎ የተከሰተው የኢቦላ ቫይረስ ከአሁን ቀደም ካጋጠመው ሁሉ የከፋ እንደሆነም ተነግሯል፡፡rnrnመንገሻዓለሙ






